No media source currently available
በኮሮና ቫይረስ ምክኒያት በእንቅስቃቄ ላይ ገደብ ከተጣለ በኋላ በትምሕርት እና በሕክምና ምክኒያት ሕንድ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በየዕለቱ ተደራራቢ ችግር እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ። 16 የሚሆኑ ተማሪዎች ፤ ከሙምባይ የሚደረግ ልዩ በረራ እንደሚኖር ሰምተው 36 ሰዓት በመኪና ተጉዘው ሲደርሱ፤ የተባለውን ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸውን ተናግረዋል።