No media source currently available
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ያለበት የመጀመሪያው ሰው ከተገኘ በኃላ፣ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል። ከነዚህ ጥረቶች አንዱ በጤና ሙያ ተመርቀው ወደ ስራ ያልተሰማሩ ባለሙያዎችን በፈቃደኝነት ተመዝግበው አገልግሎት እንዲሰጡ በማድረግ የጤና ባለሙያ እጥረትን መቅረፍ ነው።