በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጠገበ ሆድ ለሰፋ አእምሮ


የጠገበ ሆድ ለሰፋ አእምሮ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:26 0:00

የአዲስ አበባ መስተዳደር በዘንድሮ የትምህርት ዓመት ከመዋዕለ-ሕፃናት እስከ 8ኛ ክፍል ለሚገኙ300,000 ሕፃናት የቁርስ እና የምሳ መመገብ ፕሮግራም በመስከረም ወር መጨረሻ ለመጀመር ዝግጅቱን እየጨረሰ መሆኑን ይፋ አድርጕል፡፡

የአዲስ አበባ መስተዳደር በዘንድሮ የትምህርት ዓመት ከመዋዕለ-ሕፃናት እስከ 8ኛ ክፍል ለሚገኙ በ415 ት/ቤቶች ለሚገኙ 300,000ምግብ የመመገብ መርሃ-ግብር አዘጋጀቷል፡፡ በቀን በተማሪ 14 ብር ተመን በመመደብ በአጠቃላይ በጀት 4,200,000 ብር መድቦ አየሰራ ይገኛል፡፡ አንድ እናት ለ30 ተማሪዎች በማለት ለ10,000 እናቶች የስራ ዕድል መክፈቱንም አሳውቍል፡፡

በአሁን ሰዓትም የምግብ አዳራሾች፣ የማብሰያ ስፍራዎች በማዝጋጀት ላይ መሆኑን አሳውቍል፡፡ በማሕበር የተደራጁት እናቶች ስልጠና ምጨረሳቸውን ገልፆ፤ የተሻለ እና የተመጣጠነ ምግብ ማቅረብ እንዲችሉም ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የምግብ አቅራቢ ማህበራቱ ከግብር ነፃ ሆነው እንዲሰሩ እየጣረ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ ተናገረዋል፡፡

ኤደን ገረመው ተከታዩን ዘገባ አጠናቅራለች፡፡
XS
SM
MD
LG