አንድ ፓርቲ መሆን “የሚታሰብ አይደለም” - ህወሓት
ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚስተዋለው የሰላም እጦትና አለመረጋጋት ተጠያቂው የኢህአዴግ አመራር ነው ሲል የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታውቋል። ማዕከላዊ ኮሚቴው መቀሌ ላይ ለአራት ቀናት ያካሄደውን ስብሰባ አስመልክቶ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ “የግንባሩ አመራር ከፓርቲው እምነትና ፕሮግራም ውጭ እየሄደ ነውም” ብሏል ። “ኢህአዴግ ውሁድ ፓርቲ ሊሆን ነው” ስለሚባለውም ኮሚቴው ሲናገር “የግንባሩ አባል ድርጅቶች በተለያየ አቅጣጫ እየተጓዙ ባሉበት ጊዜ የማይታሰብ ነው” ብሏል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ሜይ 16, 2022
የእርዳታ አቅርቦት በትግራይ
-
ሜይ 13, 2022
በትግራይ ሰዎች በረሃብ ሲሰደዱ ህፃናት ተትተዋል
-
ሜይ 11, 2022
የኢትዮጵያ ሚዲያ ተጨማሪ ፈተናዎች