No media source currently available
በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሐዊ ጉዲና ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ የሶማሌ ክልል የታጠቁ ኃይሎች ገብተው ከ80 በላይ የአርሶ አደር ቤቶች ማቃጠላቸውንና እስካሁን ቦታውን ተቆጣጥረው መያዛቸውን የዞኑ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ተናገሩ። በሌላ በኩል ጋዱሎ በተባለ ቀበሌ ላይ በዚህ የተበሳጩ የሟች ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ሶማሌዎችን ማጥቃታቸውን መረጃ እንደደረሳቸው ተናግረዋል።