No media source currently available
የዚምባብዌው የረዥም ጊዜ መሪ ሮበርት ሙጋቤ ዋና ከተማዪቱ ሃራሬ ውስጥ “በቁም እሥር” ላይ መሆናቸውን የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ጄከብ ዙማ አረጋግጠዋል። ሮበርት ሙጋቤ ከ37 ዓመታት የፕሬዚዳንትነት ዘመን በኋላ ወታደራዊ ድጋፍ ባለው እንቅስቃሴ ዛሬ ከመንበረ ሥልጣናቸው ተገፍተው ወጥተዋል።