No media source currently available
መስከረም 23/1928 ዓ.ም (ዛሬ፤ ልክ የዛሬ 82 ዓመት) ፋሽስት ጣልያን ኢትዮጵያን ያኔ አቢሲኒያን ወረረች። ከሰባት ወራት ውጊያ በኋላ የጠላት ጦር አዲስ አበባን ያዘና የዱር የገደል ፍልሚያው ለመጭዎች አራት ዓመታት ተኩል ያህል ቀጠለ። በዚህ የያኔው የመንግሥታት ኅብረት (ሊግ አፍ ኔሽንስ) አባላት በነበሩ ሁለት ሀገሮች መካከል በተካሄደ ውጊያ ከኢትዮጵያ ከ275 ሺህ በላይ ተዋጊዎች ተገደዋል፤ ለግማሽ ሚሊዮን በላይ ጦረኞች ቆስለዋል፡፡