No media source currently available
አዲሱ የቀን ገቢ ግምት በነጋዴዎችና በግብር ሰብሳቢው መካከል የፈጠረው አለመግባባት አሁንም እንደቀጠለ ነው። የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው ነጋዴዎች በተደረገው ግምት ላይ ተቃውሞና አቤቱታ እያቀረቡ ሲሆን በአቤቱታዎቹ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙዩንኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አዲሱ አረጋን አነጋግረናቸዋል።