ተደጋጋሚው የኢንተርኔት መዘጋት - በኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ከተቋረጠ አራት ቀናት ኾኖቷል። መንግሥት አገልግሎቱ መዘጋቱን አምኖ ይህ የተደርገው ከዚህ ቀደም ያጋጠመው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መልቀቂያ ፈተና ሾልኮ እንዳይወጣና ተማሪዎች ከስጋት እና ከመረበሽ ነፃ ሆነው እንዲፈተኑ ለማስቻል እንደሆነ አስታወቋል። የዩኒቨርስቲ መምሕራን እና የድረገጽ አምደኞች ድርጊቱን ይቃወሙታል። ለተነሱ ፖለቲካዊ ችግሮች መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ቴክኖሎጂውን ማፈን መፍትሔ አይሆንም ይላሉ።
የፌስቡክ አስተያየት መስጫ