No media source currently available
የደም ልገሳን ለማጠናቀቅ፥ የተለገሰ ደምን ጤንነት ለመለየትና መድሃኒትነት ያላቸውን የደም ተዋጽኦዎች ለማቀናበር ተጨማሪ አቅም ይፈጥራል የተባለለት አዲስ የደም ማዕከል ሥራ ሊጀምር መሆኑ ዛሬ ይፋ ተደረገ። ይህ ማዕከል ለ 26 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አገልግሎት ይሰጣል ተብሏል። የማዕከሉን ሕንፃ ግንባታ ወጪ የቻለው የዩናይትድ ዓለምአቀፍ ተራድፆ መሆኑም ታውቋል።