No media source currently available
የዩናይትድ ስቴትስ ፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ከንጉስ ሳልማን ጋር ለመነጋገርና ነገ ሀሙስ ሪያድ በሚደረገው ስድስት ሃገራትን ባቀፈው የፋርስ ባህረ-ሰላጤ ሀገሮች የትብብር ካውንስል ጉባኤ ለመገኘት ሳውዲ አረብያን እየጎበኙ ነው። ባለፈው አመት ከኢራን ጋር አለም አቀፍ የኑክሌር ስምምነት ከተደረገ ወዲህ የዩናይትድ ስቴትስና የፋርስ ባህረ-ሰላጤ ሀገሮች ግንኙነት ውጥረት ሰፍኖበታል።