No media source currently available
የጋምቢያ ዲያስፖራ ማለት በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ጋምቢያውያን የፕረዚዳንት ያህያ ጃሜ መንግስት ሰላማዊ ተቃውሞ ያካሄዱ በነበሩ ሰዎች ላይ ጥቃት በመክፈት የጋምቢያውያን መሰረታዊ ሰብአዊ መብትና ህገ-መንግስታዊ መብትን ረግጠዋል ሲሉ ይከሳሉ። በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ጋምቢያውን ዲሞክራስያዊ ህብረት የተባለ ቡድን ቃል አቀባይ ፒኤ ሳምባ ጃዎ የጋምቢያ ህገ-መንግስት ሰላማዊ ተቃውሞ የማካሄድ መብት ይፈቅዳል ብለዋል።