No media source currently available
የዳርፉር ውሳኔ-ሕዝብ (Referendum)፣ ዛሬ ተጀምሯል። በዚህ ለሦስት ቀናት በሚዘልቀው ውሳኔ-ሕዝብ ዩናይትድ ስቴትስ ስጋት እንዳላት መግለጿ ታውቋል። "ውሳኔ-ሕዝቡ ተዓማኒነት አይኖረውም፣ የወቅቱን የሰላም ሂደትም ያደናቅፋል" የሚል ስጋት ነው ዩናይትድ ስቴትስ ያሰማችው። ዛሬ የተጀመረው ይህ የዳርፉር ውሳኔ-ሕዝብ፣ የክልሉን አምስት ግዛቶች የወደፊት ዕድል ይወስናል ተብሎ ይጠበቃል።