No media source currently available
የዩናይትድ ስቴስ ፕረዚዳንት ባራክ ኦባማ ትላንት ማታ ስለሀገሪቱ ሁኔታ የሚገመግመውን ሰባተኛውንና የመጨረሻውን አመታዊ ንግግር አድርገዋል። ፕረዚዳንቱ በህግ መምርያና በህግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት ፊት ቀርበው ባደረጉት ንግግር ስለመጪው አመት ብቻ ሳይሆን ስለቀጣዩቹ አምስት አመታትና ከዚያም ርቀው እንዲመልከቱ አስገንዝበዋል።