በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በትግራይ ሰብዓዊ ድጋፍ ማሰራጨት ሊቆም እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስጠነቀቀ


ምስሉ በትግራይ አጓላ በተባለ ስፍራ የረድኤት ማህበረሰብ የቀረበውን የሚሰፍሩ እናትን ያሳያል። የተነሳበት ዘመን እአአ ግንቦት 2021 ነው።
ምስሉ በትግራይ አጓላ በተባለ ስፍራ የረድኤት ማህበረሰብ የቀረበውን የሚሰፍሩ እናትን ያሳያል። የተነሳበት ዘመን እአአ ግንቦት 2021 ነው።

በትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ እንቅስቃሴ ፣ በረድዔት አቅርቦት ችግር ምክንያት ሊቋረጥ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ።

የድርጅቱ ሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ በምህጻሩ ኦቻ ፣በይዞታው ያሉ ቁሳቁሶች መመናመናቸውን ተከትሎ ፣ የጦርነት አውድማ ሆኖ በሰነበተው የሰሜን ኢትዮጵያው ትግራይ ክልል የነበረውን ሰብዓዊ ድጋፍ የማዳረስ ተግባር እንዲያቆም ሊገደድ እንደሚችል አስታውቋል ።

በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ከባድ ጦርነት እርዳታ ፣ከአውሮፓያዊኑ ታህሳስ አጋማሽ ወዲህ ለችግር ለተዳረጉ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች እንዳይደርስ ከልክሏል ።

የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጄንስ ሊያርኪ ፣ የተባበሩት መንግስታት እና ሌሎች የግል የረድኤት ተቋማት ፣ በከፋው በረድኤት ቁሳቁሶች ፣ነዳጅ እና ገንዘብ እጥረት ምክንያት እንቅስቃሴያቸውን ቀደም ባለው ጊዜ ለመቀነስ መገደዳቸውን ተናግረዋል ።

“ተቋማቱ ፣ እንቅስቃሴያቸውን (በአውሮጳዊያኑ) የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያቆሙ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል “ ያሉት ሊያርኪ ፣

"ለተጨማሪ የምገባ መርሀ ግብር ብሎም የከፋ አጣዳፊ የምግብ እጥረትን የሚፈጥራቸው ችግሮችን ለማከም የሚያስፈልጉ ምግብ ነክ ቁሳቁሶች ቀድሞውኑ አልቀዋል ” ብሏል ።

የዓለም የምግብ መርሐ ግብር 13 በመቶ ፣ከ5 ዓመት በታች የሆኑ የትግራይ ህጻናት እንዲሁም ከነፍሰጡሮች እንዲሁም ፣ እመጫት እናቶች መካከል ግማሹ በከፋ የምግብ እጥረት መጎሳቆላቸውን ጠቅሶ፣ ሁኔታው በበሽታ የመያዝን እንዲሁም ለሞት መዳረግን የሚጨምር እንደሆነ ጠቁሟል ።

ከቀናት በፊት የነደጅ ክምችት መንጠፉን ተከትሎ ፣ የረድዔት ሰራተኞች የቀረውን ድጋፍ በእግራቸው እየተዟዟሩ ለማደረስ መጣራቸውን ያስታወሱት ቃል አቀባዩ ፣ በአንጻሩ በአማራ እና አፋር ክልሎች የሰብኣዊ ድጋፍ ስርጭትን ለማዳረስ መቻላቸውን እና ወደ 380ሺ ሰዎች የምግብ እደላ አካል እንደሆኑ ተናግረዋል ።

በቅርቡ ወደ ትግራይ በአውሮፕላን ሰብዓዊ ድጋፍ የማዳረስ እርምጃ መጀመሩን ተከትሎ የድጋፉ መጠን ከፍ ማለት መጀመሩን ያወሱት ሊያርኪ ፣ ለሁኔታው የሚያስፈልገውን ከፍ ያለ መጠን ያለው ድጋፍ ግን በአውሮፕላን ብቻ ማጓጓዝ እንደማይቻል ተናግረዋል ።

XS
SM
MD
LG