በድሬደዋ ወጣቶች በበጎ ተግባራት ከተማዎን እያገዙ እንደሆነ ተነገረ

.

በድሬዳዋ ወጣት በጎ ፈቃደኞች በልዩ ልዩ ዘርፎች የአስተዳደሩን ነዋሪዎች እየደገፉ ነው ተብሏል። በአሁኑ ሰዓት 33 የአቅመ ደካማ ቤቶችን አፍርሰው እንደ አዲስ እየሰሩ ሲሆን በደም ልገሳና ችግኝ ተከላ ተግባራት ላይም ንቁ ተሳታፊ እንደሆኑ የአስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ለአሜሪካ ድምጽ አስታውቋል።

ድሬዳዋ ላይ በቅርቡ በወረርሺኝ መልኩ ሊነሱ ይችላሉ ተብለው በሚጠበቁት የደንጊ፣ ቺኩንጉንያና ወባ በሽታዎች መከላከል ዙሪያም አስፈላጊው ግንዛቤ ተሰጥቷቸው የመከላከል ስራውን ማገዝ ይጀምራሉ ተብሏል።

አዲስ ቸኮል ተጨማሪ አለው

Your browser doesn’t support HTML5

በድሬደዋ ወጣቶች በበጎ ተግባራት ከተማዎን እያገዙ ስለመሆኑ ተገለጸ