ዝዋይ ወኅኒ - የረሃብ አድማ

  • ሰሎሞን ክፍሌ

ዝዋይ

Your browser doesn’t support HTML5

ዝዋይ ወኅኒ - የረሃብ አድማ


ዝዋይ እሥር ቤት የሚገኙ የ19 ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና አንድ ጋዜጠኛ ቤተሰቦችን ጠቅሶ የወጣ የአንድ ጋዜጣ ዘገባ ታሣሪዎቹ አካሄዱ የተባለውን የረሃብ አድማ ተከትሎ ከባድ ድብደባ እንደተካሄደባቸው ይገልፃል፡፡

ድብደባ ብቻ ሳይሆን አንዳንዶቹ በጋለ ኮንቴይነር ውስጥ ተይዘዋል መባሉን አትቷል፡፡

ጉዳዩን ለማጣራት ሰሎሞን ክፍሌ ወደ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፅ/ቤትና ወደ አንድ የታሣሪ ቤተሰብ አባል ስልክ ደውሏል፡፡

የወኅኒ ቤቱን ባለሥልጣናት ለማግኘት ቢሞክርም ለጊዜው አልተሣካለትም፡፡