የሮበርት ሙጋቤ የቀብር ሥነ ስርዓት በነገው ዕለት ይፈፀማል

  • ቪኦኤ ዜና

የቀድሞው የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ

የቀድሞው የዚምባብዌ ፕሬዚዳንት ሮበርት ሙጋቤ አስከሬን በመጪው ረቡዕ ሀራሬ በሚገኘው የሮበርት ጋብሪኤል ሙጋቤ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፍያ ላይ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

ሮበርት ሙጋቤ ከረዥም ጊዜ ህመም በኋላ በ95 ዓመት ዕድሜያቸው ሲንጋፖር በሚገኝ ሆስፒታል ባለፈው አረብ ማረፋቸው የሚታወቅ ነው።

ሮይተርስ የዜና አገልግሎት በዘገበው መሰረት የሙጋቤ የቀበር ሥነ፡ስርዓት በመጪው ቅዳሜ በሀራሬ ብሄራዊ የስፖርት ስታድዮም እንደሚደረግ መንግሥት ለኤምባሲዎች መልዕክት ልኳል። የቀብር ሥነ ስርዓታቸውም በነገው ዕለት ይፈፀማል።