ሦስት ጊዜ ተፈናቅላ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ

Your browser doesn’t support HTML5

ሦስት ጊዜ ተፈናቅላ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ

በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ ውስጥ በተደጋጋሚ በተነሳው ግጭት ምክኒያት ከቤተሰቦቿ ጋራ ሦስት ጊዜ ተፈናቅላ የነበረችው ወጣት ገሊላ አሰፋ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያና ወደ ከፍተኛ ትምርት ቤት መግቢያ የላቀ ውጤት ካስመዘገቡት ሴት ተማሪዎች አንዷ ነች። በተለይ ላለፉት ሁለት ዓመታት የተረጋጋ ሕይወት እንዳልነበራት የገለፀችው ገሊላ አሰፋ በ2013 ዓ.ም አጣዬ ውስጥ የወላጆቿና የዘመዶቿ ቤቶች በሙሉ መውደማቸውን ትናገራለች።

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰች ተምራም ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች። “አስበነውም ይሁን ሳናስበው የጠበቅነውም ሆነ ያልጠበቅነው ችግሮች ያጋጥሙናል” የምትለው ገሊላ ሁሉም ነገር ያልፋል ብላ በማሰብ በፅናት መጓዟን ትናግራናለች፡፡ ገሊላን ለዛሬው የሴቶች ቀን እንግዳ አድርገናታል።

ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።