በዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ ተጀመረ

የዓየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በፓሪስ

የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ከፍተኛ ተደራዳሪዎች በሕግ ገዥ የሚሆን ስምምነት ዛሬ ፈረንሣይ ዋና ከተማ ፓሪስ ላይ ከተከፈተው የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ ይወጣል ብለው እንደሚያምኑ እየተናገሩ ነው።

የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ ከፍተኛ ተደራዳሪዎች በሕግ ገዥ የሚሆን ስምምነት ዛሬ ፈረንሣይ ዋና ከተማ ፓሪስ ላይ ከተከፈተው የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ ይወጣል ብለው እንደሚያምኑ እየተናገሩ ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ሳይቲስቶች የዓለም ሙቀት ከፍተኛው ገደብ መሆን አለበት ብለው ያወጡት ጣሪያ እስከአሁን ባለው ጥናት እጅግ የተመረጠው መሆኑን አሁንም እየተናገሩ ሲሆን በማደግ ላይ ያሉ ሃገሮች ለሚያወጧቸው ከለውጡ ጋር የመለማመጃ ስትራተጂዎች ማስፈፀሚያ የሚሆን ከለጋሾች የማገኝ ገንዘብ ምን ያህል መሆን እንዳለበት አለመቁረጣቸውን የደቡብ አፍሪካ ተደራዳሪዎች አመልክተዋል።

አኒታ ፓወል ከጆሃንስበርግ፣ አሩ ፓንዴና ክሪስ ሃንስ ከፓሪስና ዋሺንግተን ላይ ያጠናቀሯቸውን ዘገባዎችና ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ-ጳጳስ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ-የሱስ ሱራፌል ጋር ካደረገው ቃለ-ምልልስ አካቶ ሰሎሞን አካተ ተከታዩ አጠናቅሯል ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ ተጀመረ