በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እየተሰራ ነው

በጦርነቱ ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው ወደ አዲስ አበባ የመጡ የወሎና የአካባቢው ኗሪዎችን ወደ መኖሪያ ቦታቸው የመመመለስ ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ከቀያቸው ተፈናቅለው ወደ አዲስ አበባ የመጡ የወሎና የአካባቢው ኗሪዎችን ወደ መኖሪያ ቦታቸው የመመመለስ ሥራ እየተካሄደ ነው፡፡

አዲስ አበባ የሚገኘው የልዩ አውቶቡስ ትራንስፖርት ማኅበራትና ድርጅቶች የጋራ ኮሚቴ ተፈናቃዮቹን በነጻ ወደ አካባቢያቸው የመመለስ ሥራ ዛሬ የጀመረ ሲሆን አገልግሎቱ ለተከታታይ አራት ቀናት ይቀጥላል ተብሏል፡፡

በደብረ ብርሃንና በባህርዳር በተመሳሳይ ተፈናቅለው የሚገኙ ወገኖችን ወደ አካባቢያቸው እንዲገቡ የወሎ ህብረት የልማትና የበጎ አድራጎት ማኅበር ጥሪ አቅርቧል፡፡

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እየተሰራ ነው