ከመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት ጋር በተያያዘ በተፈጠረ አለመግባባት በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ግጭት መቀስቀሱ ተሰምቷል፡፡
በግጭቱ አንድ ተማሪና ሥድስት የፀጥታ ኃይሎች መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡ ዩኒቨርሲቲው መረጋጋት ቢስተዋልበትም የመማር ማስተማር ሂደቱ ተቋርጧል፡፡
ትናንትናና ዛሬ ከሰሜን ወሎ አስተዳደርና ከዩኒቨርሲቲው አካላት ጋር ውይይት ለማድረግ ቢሞከርም መግባባት ላይ አለመደረሱን ከዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ከመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረት ጋር በተያያዘ ግጭት ተቀሰቀሰ