በኖኖ ወረዳ የሠርግ ላይ ጥቃት ሙሽሮችን ጨምሮ 27 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በምዕራብ ሸዋ ዞን በኖኖ ወረዳ፣ ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ፣ በሠርግ ሥነ ሥርዓት ላይ በተፈጸመ ጥቃት 27 ሰዎች መገደላቸውንና ሌሎች 17 መቁሰላቸውን፣ በወረዳው የቢፍቱ ጃለላ ቀበሌ አስተዳዳር እና ተጎጂዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በኖኖ ወረዳ የሠርግ ላይ ጥቃት ሙሽሮችን ጨምሮ 27 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

ጥቃቱ የደረሰበት የጊፍቲ ጃለላ ቀበሌ ሊቀ መንበር አቶ ነስሩ ዑመር፣ በዕለቱ ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ በተወረወረው ቦምብ እና በተከፈተው ተኩስ ከተገደሉት ውስጥ ተጋቢ ሙሽሮችም እንደሚገኙበት ገልጸዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ የተፈናቀሉት የቀበሌው ነዋሪዎች በችግር ላይ እንደሚገኙ ያመለከተው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ወንጀሉን የሚያጣራ ቡድን ወደ ቦታው ለመላክ እየተዘጋጀ መኾኑን አስታውቋል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።