የጦርነት ወላፈን በሐይቅ

ፎቶ ፋይል፦ ሐይቅ ከተማ

የህወሓት ኃይሎች የተለያዩ የአማራ ክልል አካባቢዎችን ተቆጣጥረው በነበሩባቸው ወራት ሰላማዊ ሰዎችን እና የመኖሪያ አካባቢዎችን ዒላማ አድርገዋል ሲሉ ነዋሪዎችና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች ተናግረዋል።

በደቡብ ወሎዪቱ ሐይቅ ከተማ በአንድ መኖሪያ ቤት አባትና ልጅን ጨምሮ አራት ሰዎች በውጊያ ወቅት በተተኮሰ ከባድ መሳሪያ መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሦስቱ በአንድ ቀን የተገደሉ ሲሆን አስከሬኖቻቸውም ግቢው ውስጥ በአንድ መቃብር እንዲያርፉ መደረጉን፣ አራተኛዋ ደግሞ ህይወቷ ያለፈው በቀጣዩ ቀን በተተኮሰ ከባድ መሳሪያ መሆኑና ጦርነቱ ከተማዪቱ ውስጥ ለቀናት መካሄዱን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የጦርነት ወላፈን በሐይቅ