አዳማ ላይ የቪኦኤ ሪፖርተር ጥቃት ደረሰበት

ጋዜጠኛ ሙክታር ጀማል

“የአዳማ ፀጥታ ዛሬ የተሻለ ነው” - የከተማይቱ አስተዳደር

አዳማ ከተማ ውስጥ የተፈጠረውን ሁከትና ግጭት ሲዘግብ የነበረው የቪኦኤ ሪፖርተር ሙክታር ጀማል ጥቃት ተፈፅሞበታል፡፡

ሙክታር ጀማል በራሱ ላይ የመፈንከት ጉዳት እንደደረሰበት፣ ከንፈሩ መሰንጠቁና በጀርባውና በእግሮቹም ላይ በድንጋይ፣ በጡጫና በሌላም ማጥቂያ መደብደቡን ተናግሯል፡፡

ሙክታር ጀማል ህክምና እየተደረገለት ይገኛል፡፡

በሌላም በኩል ግን የዘጠኝ ሰው ሕይወት ከጠፋበት ሁከት በኋላ የአዳማ ፀጥታ ዛሬ የተሻለ መሆኑን የከተማይቱ አስተዳደር ለቪኦኤ አስታውቋል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

አዳማ ላይ የቪኦኤ ሪፖርተር ጥቃት ደረሰበት