በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

Your browser doesn’t support HTML5

በኢንተርኔትን ነፃነት ኢትዮጵያ ከአፍሪካ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ትገኛለች

በዲጂታል፣ ወይም በአጠቃላይ በኢንተርኔት አጠቃቀም ላይ ያለው ነፃነት ለተከታታይ 14 ዓመታት ማሽቆልቆሉን ‘ፍሪደም ሃውስ’ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ዓመታዊ ሪፖርት ላይ አመልክቷል።

በጥናቱ ከተካተቱ ሃገራት ውስጥ 41 በሚሆኑት በያዝነው ዓመት ምርጫ የሚካሄድ በመሆኑ ሁኔታውን አሳሳቢ እንደሚያደርገውና፣ ነጻና ክፍት የሆነ የኢንተርኔት አገልግሎት ዲሞክራሲ እውን እንዲሆን ወሳኝ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል።

ኢትዮጵያም በጥናቱ ከተካተቱት ሃገራት አንዷ ስትሆን፣ ኢንተርኔት ሆን ተብሎ ከሚቋረጥበት፣ የማኅበራዊ ሚዲያ ወይም ሌሎች የግንኙነት መንገዶች ከሚታገዱበት፣ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የመረጃ መረብ ላይ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ምክንያት የአካል ጉዳት ከሚደርስባቸውና ከሚገደሉበት ሃገራት ተርታ ተመድባለች፡፡

ሪፖርቱን የተመለከተው ባልደረባችን እንግዱ ወልዴ፣ ከቪኦኤዋ ቬሮኒካ ባልዴርስ ኤግሌሲያስ ዘገባ ጋራ አጣምሮ ተከታዩን አሰናድቷል።