ዛሬ ልክ የዛሬ 78 ዓመት የፋሽስት ጣልያን ወራሪ ኃይል ድል ተነስቶ ከተባረረ በኋላ ዋና ከተማዪቱን በያዘ ልክ በአምስት ዓመቱ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አዲስ አበባ ተመልሰው ገቡ።
ዋሺንግተን ዲሲ —
ኢትዮጵያን የምጣኔ ኃብት ቅኝ አድርጎ ለመያዝ ወጥኖ የነበረው የወቅቱ የጣልያን መሪ ሃሣቡ ተሣክቶለት ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያንና ግዛቱ ያደረጋትን የጣልያን ሶማሊላንድን ቀላቅሎ አሥር ሚሊየን ጣልያናዊያንን የማስፈር ሕልም ነበረው።
ዛሬ፣ ሚያዝያ 27 በኢትዮጵያ የአርበኞች፣ የድልና የነፃነት ቀን ነው። ለመላ ኢትዮጵያዊያን፣ እንዲሁም በዓለም ዙሪያ ላላችሁ የነፃነት ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን አደረሳችሁ።