ፕሬዚዳንት ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን ትናንት በዋይት ሃውስ ስላደረጉት ስብሰባ

  • ቪኦኤ ዜና

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን ትናንት ዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት ውስጥ ያደረጉት ስብሰባ "በሁለቱ ሃገሮች መካከል ለሚኖሩት ግንኙነቶች የአዲስ ዘመን መጀመሪያ ነው" ሲሉ ገልፀውታል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን ትናንት ዋይት ሃውስ ቤተመንግሥት ውስጥ ያደረጉት ስብሰባ "በሁለቱ ሃገሮች መካከል ለሚኖሩት ግንኙነቶች የአዲስ ዘመን መጀመሪያ ነው" ሲሉ ገልፀውታል፡፡

ኤርዶዋን ወደ ዋሺንግተን የተጓዙት ዩናይትድ ስቴትስ የእሥላማዊ መንግሥት ቡድን ጠንካራ ይዞታ የሆነችውን የሶሪያዪቱን ራቃ ከተማ ለመቆጣጠር እየገሰገሱ ያሉትን የኩርድ ተዋጊዎች እንደምታስታጥቅ ይፋ ካደረገች ከሁለት ሣምንታት በኋላ ነው፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ፕሬዚዳንት ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን ትናንት በዋይት ሃውስ ስላደረጉት ስብሰባ

የሶሪያ ኩርዶች ሽብርተኞች ናቸው ከምትላቸው የራሷ ኩርዶች ድርጅት ጋር ግንኙነት አላቸው የምትለው ቱርክ ሶሪያዊያኑን የማስታጠቁን ሃሣብ በብርቱ ትቃወማለች፡፡

ሌሎች የሁለቱ ሃገሮች ግንኙነት ጉዳዮች በዩኤስ-ቱርክ ጉባዔ ላይ ተመክሮባቸዋል፡፡

ዝላቲሳ ሆክ ዝርዝር አላት፤ ትዝታ በላቸው ታቀርበዋለች፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ፕሬዚዳንት ትረምፕ እና ሬሴፕ ታይፕ ኤርዶዋን ትናንት በዋይት ሃውስ ስላደረጉት ስብሰባ