የኢትዮጵያ መንግሥት የዶ/ር መረራ እስር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር የተገናኘ ነው አለ

  • እስክንድር ፍሬው

ዶ/ር ነገሬ ሌንጮ

ዶ/ር መረራ ጉዲና የታሠሩት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ክልከላ በመተላለፋቸው መሆኑን የገለፁት የመንግሥቱ ቃል አቀባይ ተጨማሪ መረጃ በሂደት ሊገኝ የቻለው ከሕግ አካላት ወይንም ከማዘዣ ጣቢያው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

“ኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን እያሰረች ነው” የሚለው አባባልም ያለውን ሁኔታ አያንፀባርቅም ሲሉ ተችተዋል፡፡

ዶ/ር ነገሬ ሌንጮ ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ለሚገኙ የውጭ ሀገር የዜና ወኪሎች መግለጫ የሱጡ ሲሆን፣ በመግለጫቸው ከሁለት ቀናት በፊት የታሠሩት የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ መስራችና ሊቀመንበር እንደዚሁም የመድረክ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ ማብራሪያ አልሠጡም፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

የኢትዮጵያ መንግሥት የዶ/ር መረራ እስር ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጋር የተገናኘ ነው አለ