ባይደን በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ጣሉ

Your browser doesn’t support HTML5

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ሩሲያ ዓለም አቀፉን ሕግ በመጣስ ዩክሬንን መውረር ጀምራለች በሚል፣ ሩሲያን ከምዕራቡ ዓለም የፋይናንስ መረብ ነጥለዋል። በትላልቅ ባንኮቿም ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።

ዩናይትድ ስቴትስ፣ አውሮፓ ሕብረት፣ እንግሊዝ፣ ካናዳና ጀርመን ትናንት በወሰዱት እምርጃ ከፍተኛ ማዕቀብ መጣላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ዩክሬን ውሳኔውን ደግፋ ማዕቀቡ ፑቲንን ከቀጣይ እምርጃዎቻቸው ሊያስቆማቸው የሚገባ መሆን እንዳለበት አሳስባለች።