የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የሩስያ አቻቸውን አነጋገሩ

  • ቪኦኤ ዜና
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የሩስያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭን ዋሺንግተን ላይ ዛሬ - ረቡዕ ቢሯቸው ተቀብለው አነጋግረዋቸዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የሩስያ አቻቸው ሰርጌይ ላቭሮቭን ዋሺንግተን ላይ ዛሬ - ረቡዕ ቢሯቸው ተቀብለው አነጋግረዋቸዋል።

የሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ውይይት በአመዛኙ ያተኮረው በሶሪያና በዩክሬይን ላይ ሲሆን ጉዳዮቹን በተመለከተ በሁለቱ ሃገሮች መካከል ያሉ ልዩነቶች እንደተጠበቁ መሆናቸው ተገልጿል።

የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ ዋሺንግተንን ሲጎበኙ ባለፉት ዓመታት ሦስት ዓመታት ይህ የመጀመሪያ ጊዜያቸው ነው።

ሁለቱ ሚኒስትሮች በመቀጠል አርክቲክ ካውንስል በሚባለው የአርክቲክ አካባቢ መንግሥታትና ህዝቦች ጉዳዮች ላይ በሚመካከረው ኅብረ መንግሥታዊ ስብስብ ጉባዔ ላይ ለመገኘት ወደ አላስካ ይጓዛሉ።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን የሩስያ አቻቸውን አነጋገሩ