ባራክ ኦባማ "የፅናት ተምሳሌት" ሽልማት ተቀበሉ

  • ሔኖክ ሰማእግዜር

የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ

የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ትላንት ዕሁድ ባደረጉት ንግግር የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ከፓርቲያቸው አቋም ጋር ቢጣረስም ዕውነቱን መርምረው ሃቅ እንደሚናገሩ ጥልቅ ምኜቴ ነው ብለዋል፡፡

የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ትላንት ዕሁድ ባደረጉት ንግግር የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት አባላት ከፓርቲያቸው አቋም ጋር ቢጣረስም ዕውነቱን መርምረው ሃቅ እንደሚናገሩ ጥልቅ ምኜቴ ነው ብለዋል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያው ጥቁር ፕሬዚዳንት ትላንት ይህን አስተያየት የሰጡት ቦስተን ከተማ ውስጥ የጆን ኤፍ ኬኔዲን ተቋም "የፅናት ተምሳሌት" በሚል ርዕስ የሚጠራውን ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት ነው፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

ባራክ ኦባማ "የፅናት ተምሳሌት" ሽልማት ተቀበሉ

የኦባማ አስተያየት የተሰማው የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ከክንዋኔዎቻቸው በዓይነተኛነቱ ተልይቶ የሚታወቀውን የሀገሪቱን የጤና ምርሃ ግብር የሚተካ አዲስ ፖሊሲ ባፀደቀ ከጥቂት ቀናት በኋላ መሆኑ ነው፡፡

ኦባማ በርሳቸው አስተዳደር የፀደቀና በስማቸው የሚጠራ የጤና ፖሊሲ ለመሻርና ለመተካት ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙትን ተተኪያቸውን ዶናልድ ትራምፕን በስም ከመጥራትም ሆነ እርሳቸውን ከማመላከት ተቆጥበዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ባራክ ኦባማ "የፅናት ተምሳሌት" ሽልማት ተቀበሉ