ሰሜን ኮርያ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በመጪው ቅዳሜ በኒኩሌር ጉዳይ ላይ ንግግር ለማድረግ እንደተስማማች አንድ የሰሜን ኮርያ ዲፕሎማት በመንግሥት ሚድያ መናገራቸው ተጠቅሷል።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የሰሜን ኮርያ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺኦስ ሰን ሁይ ፕዮንግ ያንግና ዋሺንግተን በመጪው ቅዳሜ ተገናኝተው ለመነጋገር ተስማምተዋል ብለዋል። በዋዜማው “ቀዳሚ ግንኙነት” ይደረጋል ሲሉ አክለዋል። የስብሰባው ቦታ የት እንደሆነ ግልፅ አይደልም።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕና የሰሜን ኮርያው መሪ ኪም ዦንግ ኡን፣ ሁለቱን ኮርያዎች በሚለየው ከወታደራዊ ህልውና ነፃ በሆነው ቀጠና ተገናኝተው ከተነጋገሩ ሦስት ወራት በኋላ ነው በመጪው ቅዳሜም እንደሚገናኙ የተገልፀው።