ዩክሬን እና ቻይና የኔቶ 75ኛ ዓመት የመሪዎች ጉባኤ አብይ ትኩረት ሆነው ሰንብተዋል

  • ቪኦኤ ዜና

በዋሽንግተን ዲሲ ጉባኤ በማድረግ ላይ ያለው የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ጉባኤ

Your browser doesn’t support HTML5

ዩክሬን እና ቻይና የኔቶ 75ኛ ዓመት የመሪዎች ጉባኤ አብይ ትኩረት ሆነው ሰንብተዋል

የኔቶ አጋሮች በትላንትናው ዕለት ሩሲያ በዩክሬይን በምታካሂደው ጦርነት ቻይና የምትሰጠውን እገዛ እንድታቆም እና ኪቭ ኔቶን እንድትቀላቀል በሚያስችላት ጎዳና የማይታጠፍ ድጋፋቸውን ለመስጠት ቃል ገብተዋል። ይህም የዩክሬይንን የአየር ክልል የሚያስጠብቁ አዳዲስ ተዋጊ ጄቶች በዩክሬይን ሰማይ የሚበሩበትን ጊዜ ይጨምራል። በተያያዘ ዜና የኔቶ እና የዩክሬይን መሪዎች ዛሬ ሐሙስ ዋሽንግተን ላይ ተገናኝተው ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የአሜሪካ ድምጿ የፔንታገን ዘጋቢ ካርላ ባብ ያደረሰችንን ዘገባ አሉላ ከበደ ወደ አማርኛ መልሶታል።