የዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር የማዕከላዊ አሜሪካ ፍልሰተኞች በአሜሪካ ጥገኝነት እንዳይጠይቁ ለማገድ በቀናት ውስጥ ከጓቲማላ ጋር ሥምምነት የማድረግ ተስፍ እንዳለው ገልጿል።
ዋሺንግተን ዲሲ —
የዋይት ሃውስ ቤተ መንግሥት ያረቀቀው ገና ያልተፈረመ ባለ ሰባት ገፅ የሥምምነት ዕቅድ ሃሳብን የአሜሪካ ድምፅ አግኝቷል።
በዩናይትድ ስቴትስና በጓቲማላ መካከል “የአስተማማኝ ሦስተኛ ሃገር” ፕሮቶኮል ይመሰርታል። ረቂቀ ሃሳቡ በያዝነው ሳምንት ለጓቲማላ መንግሥት ይቀርባል።