ከዩናዩትድ ስቴትስ ከ1 ሚሊዮን በላይ የኮቪድ-19 ክትባቶች ኢትዮጵያ ደረሱ

  • ቪኦኤ ዜና

ኢትዮጵያ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ

በኢትዮጵያ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ከዩናይትድ ስቴት በኮቫክስ በኩል የተላኩ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የፋይዘር የኮቪድ-19 ክትባት መድሃኒቶች ኢትዮጵያ መድረሳቸውን በኢትዮጵያ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ፡፡

ይህ እኤአ ከሀምሌ 2021 ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ የተላከውን የፋይዘር የኮቪድ-19 ክትባት መጠን ወደ 4 ሚሊዮን የሚያደርሰው ሲሆን ከአንድ አገር ብቻ ወደ ኢትዮጵያ ከተላኩት ክትባቶች ውስጥ ከፍተኛው እንደሆነ ኤምባሲው አስታውቋል፡፡