ዕገዳ የተጣለባቸው ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ ሰባ ሰዎች ከኢትዮጵያ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጓዙ

  • እስክንድር ፍሬው

United Nations High Commissioner for Refugees logo

ዕገዳ የተጣለባቸውን ሀገራት ዜጎች ጨምሮ ሰባ ሰዎች ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ መጓዛቸውን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ዕገዳ የተጣለባቸውን ሀገራት ዜጎች ጨምሮ ሰባ ሰዎች ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ መጓዛቸውን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በአዲስ አበባ የድርጅቱ ቃል አቀባይ አቶ ክሱት ገ/እግዜብሄር እንዳሉት ሰዎቹ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የገቡት በፕሬዚዳንት ትራምፕ ያስፈፃሚ ትዕዛዝ ምክንያት በረራቸው ተሰርዞ ከቆየ በኋላ ነው፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን የኢትዮጵያ ቃል አቀባይ ክሱት ገ/እግዜብሄር በስልክ ለአሜሪካ ድምፅ እንዳብራሩት እአእ በ2017፤ ሰባት ሺሕ አምስት መቶ የጎረቤት ሀገራት ስደተኞችን ከኢትዮጵያ ወደ ተቀባይ ሀገራት ለመላክ ታቅዷል፡፡ በዚህም መሠረት በዓመቱ የመጀመሪያ ጥር ወር 2017፣ ሦስት መቶ አራት ስደተኞች ጥገኝነት ሊሰጡዋቸው ወደ አቀዱ ሀገራት መጓዛቸውን ገልፀዋል፡፡

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ዕገዳ የተጣለባቸው ሀገራት ዜጎችን ጨምሮ ሰባ ሰዎች ከኢትዮጵያ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጓዙ