በኢትዮጵያ ለሚገኙት የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ ፊልፖ ግራንዲ ማብራሪያ ተሰጣቸው

  • መለስካቸው አምሃ

በተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ እና የሰላም ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፍሪሃት ካሚል

የኢትዮጵያ መንግሥት በሰላም ሚኒስቴር አማካኝነት በትግራይ ክልል ስላለው የሰብዓዊ ሁኔታ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማብራሪያ መስጠቱ ተገለፀ። የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሙፈሪያት ከሚል፤ መሥሪያ ቤታቸው በኢትዮጵያ ለሚገኙት ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ ፊልፖ ግራንዲ የተሰጠውን ማብራሪያ በተመለከተ ለጋዜጠኞች በሰጡት አጠር ያለ ገለፃ ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ ክልል ሕግን ለማስከበር ከወሰደው እርምጃ በኋላ በሰብዓዊ ሁኔታው ዙሪያ እየተከናወኑ ነው ያሉትን ሥራ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኃላፊዎች አስረድተዋል።

በተለይም በኢትዮጵያ በአራት የስደተኛ ማቆያ መጠለያ ውስጥ ስለሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኖች ማብራሪያ ተሰጥቷል ብለዋል። ኮሚሽነሩም የተሠሩ ሥራዎችን በአካል ተገኝተው እንደሚመለከቱ ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ ለሚገኙት የስደተኞች ጉዳይ ኃላፊ ፊልፖ ግራንዲ ማብራሪያ ተሰጣቸው