79ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ

Your browser doesn’t support HTML5

79ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ

79ኛው የመንግሥታቱ ድርጅት ጉባኤ ከተጀመረ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ “ማንንም ወደኋላ ሳንተው ለሠላም ለዘላቂ ልማት እና ለሠብዓዊነት እድገት እንሰራለን” የሚል መሪ ቃል አንግቧል፡፡

በሁለተኛው ቀን ጉባኤ ላይ ሊቢያ፣ ላይቤሪያ፣ ናሚቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ንግግር ካደረጉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል ናቸው፡፡ የፈረንሳይ እና የዩክሬንም መሪዎችም በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት ንግግር አድርገዋል፡፡

የብዙዎችን ትኩረት የሳበ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚደንት ዘለንስኪ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት፣ ዩክሬን በጎርጎርዮሳዊያኑ 2014 በሩሲያ የተጠቃለለችባትን ክሬሚያን ሳታስመልስ አያቆምም ብለዋል፡፡