ለሽብር ውጊያ ወደ ኢራቅና ሶሪያ የሚጓዙ ወዶ ዘማቾችን እንቅስቃሴ የሚገድብ አዲስ ኅግ፤

U.S. President Barack Obama chairs the U.N. Security Council summit in New York September 24, 2014. REUTERS/Kevin Lamarque (UNITED STATES - Tags: POLITICS) - RTR47L4F

Your browser doesn’t support HTML5

ለሽብር ውጊያ ወደ ኢራቅና ሶሪያ የሚጓዙ ወዶ ዘማቾች


የሌሎች ሃገሮች ዜጎች የሆኑ ወይም ከሌሎች ሃገሮች የሚነሱ የሽብር ተዋጊዎች ወደ ሶሪያና ኢራቅ እንዳይገቡ ወይም ከዚያ እንዳይወጡ የሚያግድ ውሣኔ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አፅድቋል፡፡

በመካከለኛው ምሥራቅና በሌሎችም አካባቢዎች ሽብርተኞች ግጭቶችን እያባባሱ መሆናቸውን ያመለከተው የጸጥታው ምክር ቤት ጉባኤ፤ በተለያዩ በርካታ አጋጣሚዎች እንደታዩትም ወደየተነሱባቸው ሃገሮች እየተመለሱ ለብዙዎች ሕይወት የመጥፋት አደጋ ሥጋት መደቀናቸውን ገልጧል።፡

ምክር ቤቱ ውሣኔውን ያሳለፈው ትናንት ከቀትር በኋላ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን ባካሄደው ልዩ ስብሰባው ነው፡፡ ዝርዝሩን ከዘገባው ይከታተሉ።