በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት አሠቃቂ ወንጀሎች ስጋት እንደጨመረ ተመድ አስጠነቀቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት አሠቃቂ ወንጀሎች ስጋት እንደጨመረ ተመድ አስጠነቀቀ

የኢትዮጵያ መንግሥት፣ በልዩ ልዩ ክልሎች ውስጥ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋራ የገባበት የትጥቅ ግጭት መቀጠሉን ተከትሎ፣ በአገሪቱ ውስጥ፥ የዘር ማጥፋት እና ተዛማጅ አሠቃቂ ወንጀሎች የመፈጸማቸው ስጋት በከፍተኛ ኹኔታ እንደጨመረ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ምክትል ዋና ጸሐፊ እና ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሪሙ ንደሪቱ አስጠነቀቁ።

የትግራይ፣ የዐማራ፣ የአፋር እና የኦሮሚያ ክልሎች፣ የትጥቅ ግጭቶች እንደቀጠሉባቸው፣ በመግለጫው የተጠቀሱ አካባቢዎች ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም በበኩላቸው፣ መግለጫው፥ “ሓላፊነት የጎደለው ነው፤” በማለት አጣጥለውታል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።