ዛሬ ጥር 29 በሴት የመራቢያ እና የፆታ አካላት ላይ የሚፈፀም ማንኛውም ጉዳት ይህም ማለት ግርዛት፣ መተልተል፣ መስፋት የመሳሰሉ ኢ - ሰብዓዊ አድራጎቶችን የመቃረኛ፣ የማውገዣ፣ ዓለም አቀፍ ቀን ነው፡፡
ዋሺንግተን ዲሲ —
እንደዚህ ዓይነቶቹን ስብዕና የጎደላቸውና የጭካኔ ድርጊቶች ችላ ልንል ፈፅሞ አይበገባንም - ይላል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት - ፈጽሞ ዜሮ ቶሎራንስ ይለዋል የመንግሥታቱ ድርጅት፡፡
የዓለም የጤና ድርጅት በዌብሳይቱ ላይ ባሠፈረው ፅሁፍ የዚህ ዓመቱን መሪ ቃል በተለይ ከአፍሪካ ጋር አያይዞታል፡፡
"በሴት የጾታ አካላት ላይ የሚፈፀምን ማንኛቸውንም ዓይነት ጉዳት በ2022 ዓ.ም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ወይም በአውሮፓ 2030 ዓ.ም ከዓለም ጨርሶ ለማስወገድ በአፍሪካና በሌላው ዓለም መካከል ጠንካራና የጋራ መስተጋብር መፍጠር የሚያስችል ድልድይ መገንባት" የሚል ነው መሪ ቃሉ በአማረኛ ዘርዘር ተድረጎ ሲነገር፡፡
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።
Your browser doesn’t support HTML5
የሴት የፆታ አካላት ከጉዳት ይጠበቁ