በኢትዮጵያ እየተባባሰ ለመጣው የምግብ ዋስትና እጦት የ17 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊዝስ አስታወቁ። አዲስ የተመደበው ይህ የገንዘብ ድጋፍ ኢትዮጵያን ለተጨማሪ አደጋ ያጋለጠው ‘ኤልኒኞ’ የአየር መዛባት ያስከተለው ድርቅ በአፋር፣ በአማራ እና በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች የከፋ ጉዳት ሊያስከትል መቻሉ ያሳደረውን ብርቱ ስጋት የሚያንጸባርቅ ነው ተብሏል።
The El Niño-driven drought and ongoing hostilities are threatening the food security of millions in #Ethiopia.There is a short window of opportunity to avert a greater crisis.I%27m allocating $17M from @UNCERF to urgently scale up the response. pic.twitter.com/mbxcN54MIG
— Martin Griffiths (@UNReliefChief) February 27, 2024
ኢትዮጵያን የገጠመው የምግብ ዋስትና እጦት በመጭው ወራትም እየበረታ ሊሄድ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት የክረምት ወራት ውስጥ በመላው ኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ተጨማሪ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከዚህ ቀደም የተከሰተው ድርቅ እና በሃገሪቱ ያሉት ግጭቶች አሁንም ተጽዕኖ ማሳደራቸውን ቀጥለዋል። በሌላ በኩል የጎርፍ መጥለቅለቅ ተጨማሪ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ተጠቁሟል።
The Govt of #Eth & #humanitarian partners released the 2024 Humanitarian Response Plan today. US$3.24 billion required for food, non-food & protection assistance to 15.5 million people affected by #drought, #flood, #hostility & #outbreaks. More on: https://t.co/RY71Tosesg
— UN OCHA Ethiopia (@OCHA_Ethiopia) February 26, 2024
ከ2013 እስከ 2015 ባለው ጊዜ በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደውን ጦርነት ጨምሮ በሃገሪቱ በተከታታይ ለደረሱ ምስቅልቅል ሁኔታዎች የተጋለጡ ማሕበረሰቦችን ከገጠማቸው የከፋ ጉዳት ለመታደግ ያለው ዕድል አጭር ዕድሜ ዘላቂ መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት አመልክቷል።