በትግራይ ክልል ተጨማሪ የአየር ጥቃት መድረሱ ተገለፀ

ፎቶ ፋይል፦ መቀሌ

የኢትዮጵያ መንግሥት ትናንት እሁድ ጥቅምት 14 /2014 ዓ.ም በትግራይ ክልል በዓድዋና በማይፀብሪ በፈፀመው የአየር ጥቃት ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጉዳት አድርሷል ሲሉ በአሁኑ ሰዓት የክልሉ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ መሆናቸውን የሚናገሩት ወ/ሮ ሊያ ካሳ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግሥት የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ የትናንቱ የአየር ድብደባ ለወታደራዊ ጥቅም የተዘጋጁ ስፍራዎች ላይ ብቻ ያነጣጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ፡፡

Your browser doesn’t support HTML5

በትግራይ ክልል ተጨማሪ የአየር ጥቃት መድረሱ ተገለፀ