ትረምፕ ሜክሲኮ እና ካናዳ ላይ የተጣለውን ቀረጥ ለአንድ ወር አዘገዩ

  • ቪኦኤ ዜና

Your browser doesn’t support HTML5

ትረምፕ ሜክሲኮ እና ካናዳ ላይ የተጣለውን ቀረጥ ለአንድ ወር አዘገዩ

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትረምፕ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በካናዳ ሜክሲኮ እና ቻይና ላይ አዲስ ቀረጥ እንደሚጣል ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ትላንት በዓለም ዙሪያ የአክሲዮን ገበያ ዋጋ አሽቆልቁሏል። ሆኖም ፕሬዝደንቱ በሜክሲኮ እና በካናዳ ላይ የተጣሉት ቀረጦች ለአንድ ወር እንደሚያዘገዩላቸው ይፋ ካደረጉ በኋላ የገበያው ዋጋ በተወሰነ ደረጃ አንሰራርቷል። በሌላ በኩል ከቻይና በሚገቡ ምርቶች እና ሸቀጦች ላይ የተጣለው ተጨማሪ ቀረጥ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል። ቻይና በበኩሏ ከዩናይትድ ስቴትስ በሚገቡ ምርቶች ላይ ተጨማሪ ቀረጥ እንደምትጥል አስታውቃለች።

አኒታ ፓወል ከኋይት ሐውስ ያጠናቀረችው ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።