የኢራን ድብደባ - የትራምፕ እና የዓለም ምላሽ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ

ኢራን የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በሚገኙባቸው የኢራቅ የጦር መደቦች ላይ የሚሳየል ጥቃት ካደረሰች በኋላ ዛሬ ረፋድ ላይ ከዋይት ሃውስ የተናገሩት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ አንደበታቸው በአመዛኙ የተለሳለሰ ነበር።

የጦር ኃይላቸውን ጥንካሬና የሀገራቸውን ምሳሌ ኃብት በአጽንኦት በተናገሩበት ለዘጠኝ ደቂቃዎች የዘለቀ ንግግራቸው፤ በከርሰ ምድር ዘይትና በጋዝ ምርት ከየትኛውም የዓለም ሀገር የቀደምን በመሆናችን ስለዚህ ጉዳይ መካከለኛው ምሥራቅ እምብዛም አያሰጋንም ብለዋል።

የዛሬው የኢራን ጥቃት ያደረሰው የከበደ ጉዳት እንደሌለም ፕሬዚዳንት ትራምፕ ተናግረዋል።

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ