ትረምፕ በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ላይ ዘለፋ ሰነዘሩ

  • ቪኦኤ ዜና
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ በፈረንሳይና በመሪዋ በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ላይ ዘለፋ ሰንዝረዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትረምፕ ዛሬ በፈረንሳይና በመሪዋ በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ላይ ዘለፋ ሰንዝረዋል። ፕሬዚዳንት ማክሮንን ዝቅ ያለ የሕዝብ ድጋፍ ያላቸው ያሉዋቸው ሚስተር ትረምፕ ፈረንሳይ ከዩናይትድ ስቴትስ በሚላኩ የወይን ጠጆች ላይ ቀረጥ በመጣሏ ነቅፈውታል።

ሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት /ኔቶ /መደበውን የአባል ሃገሮች የመከላከያ ወጪ በጀት ማሙዋላት ያቃታት ሲሉ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚደንት ፈረንሳይን ነቅፈዋታል።