የህወሓት ድርጅታዊ ጉባዔ ተጠናቀቀ

13ኛ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ድርጅታዊ ጉባዔ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ሊቀመንበር በማድረግ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

13ኛ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ድርጅታዊ ጉባዔ ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ሊቀመንበር በማድረግ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
በጉባዔው 55 የማዕከላዊ ኮሚቴ ተመርጧል። ከእነዚህ 30ዋቹ ለኮሚቴው አዲስ ናቸው።
የኮሚቴው አባላት ከዚህ ቀደም ከነበሩ 45 ወደ 55 ቁጥሩ እንዲጨምር የተደረገ ሲሆን የሥራ አስፈፃሚ አባላትም ከ9 ወደ 11 እንዲሆን ተደርጓል።
12 ነባር አመራሮች የማዕከላዊ ኮሚቴ በክብር ከኮሚቴው ተሰናብተዋል። በዚህ ጉባዔ የድርጅቱ ህገ ደንብ ተሻሽሏል። በዚህ መሰረት የህወሓት አባል ለመሆን የትግራይ ተወላጅ ብቻ ሳይሆን የሌላ ክልል ተወላጆችም የፓርቲው መሥመር ካመነበት አባል መሆን ይችላል ተብሏል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

Your browser doesn’t support HTML5

የህወሓት ድርጅታዊ ጉባዔ ተጠናቀቀ