የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የህዝብና ቤት ቆጠራ መራዘሙን ተቃወመ

አቶ አብርሃም ተከስተ

አራተኛው ዙር ሀገርቀፍ እንዲራዘም የቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተገቢ አይደለም ሲል የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ።

የመንግሥት ተዓማኒነትን የሚሸረሽር እንዲሁም ሕገ መንግሥቱን የሚፃረር ነው በማለት ትክክል አይደለም ብሎ የክልሉ መንግሥት እንደሚያምን በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የትግራይ ክልል ንግድ፣ ኢንዳስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር አቶ አብርሃም ተከስተ በትናንትናው ዕለት በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

የፌደራል የህዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው የመመለስ ሥራ በሚፈለገው ሥራ ስላልተፈፀመ የቆጠራ ሥራው ይራዘም የሚል የውሳኔ ሐሳብ ማቅረቡ ይታወሳል።

ለተጨማሪ ዘገባ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Your browser doesn’t support HTML5

የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የህዝብና ቤት ቆጠራ መራዘሙን ተቃወመ