በራያ ዓዘቦ ወረዳ የሰባት ሲቪሎች ግድያ ፍትሕ እንዲረጋገጥ አስተዳደሩ ጠየቀ

Your browser doesn’t support HTML5

በራያ ዓዘቦ ወረዳ የሰባት ሲቪሎች ግድያ ፍትሕ እንዲረጋገጥ አስተዳደሩ ጠየቀ

ከትላንት በስቲያ ሰኞ፣ በራያ ዓዘቦ ወረዳ በተፈጸመው የሰባት ሲቪሎች ግድያ ፍትሕ ብንጠብቅም፤ አሁንም፣ በአዋሳኝ አካባቢ የሚገኙ የአፋር ታጣቂዎች፥ ምሽግ ቆፈረው ለግጭት እየተዘጋጁ ነው፤ ሲሉ፣ የራያ ዓዘቦ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአሜሪካ ድምፅ ገልጸዋል።

በጉዳዩ ላይ፣ ከአፋር ክልል አዋሳኙ መጋላ ወረዳ እና ከአፋር ክልል መንግሥት፣ እንዲሁም ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ስልክ በመደወልና የጽሑፍ መልእክት በመላክ ምላሽ እና ማብራርያ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።